
በአዲስ አበባ ከተማ በዝቅተኛ ግብር ከፋዮች ላይ የተጣለው አዲሱ የቀን ገቢ ግብር ትመና “ከገቢያችን ጋር በፍጹም የማይገናኝና ከሥራ ውጭ የሚያደርገን ነው” ሲሉ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች አማረሩ።“ምሬታችንንም የሚሰማን አጥተናል” ብለዋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮችን ጨምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ይመለከታቸዋል ያልነውን የገቢ ግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤቶች ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
Source: amharic.voanews.com




